ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ጀምሮ የሊበራሊዝም አስተሳሰብ በበርካታ የዓለም ሀገራት ዘንድ ተቀባይነቱ እየጨመረ እንደመጣ ይታመናል፡፡ የሊበራል አስተሳሰብ በዋናነት ለዜጎች የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነት ትኩረት የሚሰጥ፣ የመንግስትን መጠንና ጣልቃ ገብነት በመገደብ ዜጎች በግልም ሆነ በጋራ በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ እድል የሚሰጥ ስርአት ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ የተንዛዛ የመንግስት አሰራርን፣ ቢሮክራሲያዊ ንቅዘትን፣ የመንግስትን አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነት ለማስቆም፣ ሙስናን በማስወገድ ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራር እውን ለማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የዜጎችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት በተሻለ ሁኔታ ለማስከበር ይረዳል ተብሎ ይገመታል፡፡ የሊበራል አስተሳሰብ ሰፊ ፅንሰ ሀሳብ ሲሆን፣ እንደ ሀገራት የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ የባህልና የቴክኖሎጂ እድገት ደረጃ በተለያየ መንገድ የሚተገበርና አንድ ወጥ መለኪያ የሌለው መሆኑ፤ እንደ ሀገራቱ ተጨባጭ ሁኔታ ሊስተካከል መቻሉ ተቀባይነቱን ሊጨምር እና አተገባበሩም ምቹ እንዲሆን አስችሏል፡፡
በዚህ መሰረት የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ራእዩን በተሳካ ሁኔታ እውን ለማድረግና ዓላማዎቹን ለማሳካት የሊበራል አስተሳሰብን ከሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ጋር አዋዶ ነባራዊ እና ተጨባጭ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ እውነታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለዘብተኛ ሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ይከተላል፡፡ የለዘብተኛ ሊበራል ርዕዮተ ዓለም የሊበራል አስተሳሰቦችን ከሀገራችን ታሪክ፣ ባህል፣ የህዝቦቿ ስነ-ልቦናና ማህበራዊ ልማዶች ጋር በማዋደድ ሀገራዊ እሴቶችን ለመጠበቅ ምቹ የፖለቲካ ምህዳር እንደሚፈጥር ይታመናል፡፡ የለዘብተኛ ሊበራል አስተሳሰብ ለማህበራዊ እሴቶችና ግብረገብነት እውቅና የሚሰጥ ሲሆን የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ በማድረግ ለላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ይጠበቃል፡፡ ነእፓ በዋነኛነት ከሚከተለው የለዘብተኛ ሊበራል ርዕዮተ ዓለም በተጨማሪ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የሶሻል ዴሞክራትን ጨምሮ ሌሎች ርዕዮተ-ዓለማዊ አስተሳሰቦችን መሰረት ያደረጉ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ርዕዮተ-ዓለምን በተመለከተ ፓርቲያችን የሚከተለው ይህ አሰራር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ከነገሰው በአንድ ርዕዮተ-ዓለም የመታጠር ጠባብ የፖለቲካ አረዳድ ወጣ ባለ መንገድ ከሊበራል አስተሳሰብ ጋር የማይጋጩ፣ የሀገራችንን የእድገት ደረጃ ታሳቢ ባደረገ መንገድ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና የሚያግዙ ሰፊ የፖሊሲ አማራጮችን ለማሰብ ይረዳል ተብሎ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄሮች/ብሄረሰቦች፣ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች፣ ባህሎች፣ ወጎችና ልማዶች፣ ኃማኖቶችና ማህበራዊ እሴቶች ያሏቸው ህዝቦች መኖሪያ ናት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ ብዝሃ ህይወት፣ መልክአ ምድር፣ የአየር ጸባይና የአኗኗር ዘይቤዎች ላይ የተመሰረተ የማህበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ብዝሀነት ያሏት ሀገር ናት፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚዘረጋ የመንግስት አወቃቀር እነዚህን የሀገራችንና የህዝባችንን ተፈጥሯዊ ልዩነቶችና ብዝሀነት ታሳቢ ያደረገ፣ በአንድነት ውስጥ ልዩነትን ማስተናገድ የሚያስችል፣ በመፈቃቀድ፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ የተመሰረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆን ይኖርበታል፡፡
ነእፓ ለዚህ ዓላማው እውን መሆን የተሻለው የመንግስት አወቃቀር የፌደራል ስርአት ነው ብሎ ያምናል፡፡ እውነተኛ የፌደራል መንግስት አወቃቀር ሁሉም የሀገራችን ህዝቦች በስምምነት በመከባበር ተፈቃቅደው ለመኖር የሚያስችል ምቹ አስተዳደራዊ ስርአት ይፈጥራል፡፡ የሚገነባው የፌደራል ስርአት የአስተዳደር ምቹነትን፣ የህዝብ ፍላጎትን፣ ቋንቋና ባህልን፣ መልከዓ-ምድርንና ሌሎች የጋራ እሴቶችን ታሳቢ ያደረገ ይሆናል፡፡
ፓርቲያችን የሚከተለው የመንግስት ስርዓት ፕሬዚዳንታዊ ይሆናል፡፡ ፕሬዝደንቱ (ርዕሰ ብሄር) በቀጥታ በህዝብ የሚመረጥ ሲሆን ለአምስት ዓመታት ያገለግላል፡፡ አንድ ፕሬዝደንት ለሁለት ዙር መወዳደር ይችላል፡፡
ሕገ-መንግስት የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች እንዲሁም የመንግስትን አወቃቀርና አሰራር የሚወስኑ መሰረታዊ ህጎችና መርሆችን የሚይዝ የህግ እና የፖለቲካ ሰነድ ሲሆን በአንድ ሀገር ውስጥ የሚወጡ ህጎች፣ መመሪያዎች፣ ደንቦች፣ ፖሊሲዎች ወዘተ መነሻ ነው፡፡ሕገ-መንግስት መሰረታዊ የሆኑ የፖለቲካ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የውጭ ግንኙነት መርሆችን የሚይዝ ለአንድ ሀገር ሰላምና ብልጽግ እንዲሁም ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ አንድነት፣ ነጻነት፣ እኩልነትና ፍትህ ዋስትና የሚሰጥ የዜጎች የመግባቢያ ሰነድ ነው፡፡ሕገ-መንግስት እንደ ስሙ የሀገርና የመንግስት ህግ ይሆን ዘንድ በአብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ተቀባይነት ያለው፣ ግልጽና የማያሻማ ሊሆን ይገባል፡፡ ከዚህ አንጻር የሀገራችንን ሕገ መንግስት ስንመለከተው መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡ በመሆኑም ነእፓ በስራ ላይ ያለው የሀገራችን ሕገ-መንግስት የሚከተሉትን ነጥቦች ከግምት ዉስጥ በማስገባት መሻሻል አለበት ብሎ ያምናል፡፡
ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄሮች/ብሄረሰቦች፣ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች፣ ባህሎች፣ ወጎችና ልማዶች፣ ኃማኖቶችና ማህበራዊ እሴቶች ያሏቸው ህዝቦች መኖሪያ ናት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ ብዝሃ ህይወት፣ መልክአ ምድር፣ የአየር ጸባይና የአኗኗር ዘይቤዎች ላይ የተመሰረተ የማህበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ብዝሀነት ያሏት ሀገር ናት፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚዘረጋ የመንግስት አወቃቀር እነዚህን የሀገራችንና የህዝባችንን ተፈጥሯዊ ልዩነቶችና ብዝሀነት ታሳቢ ያደረገ፣ በአንድነት ውስጥ ልዩነትን ማስተናገድ የሚያስችል፣ በመፈቃቀድ፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ የተመሰረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆን ይኖርበታል፡፡
ነእፓ ለዚህ ዓላማው እውን መሆን የተሻለው የመንግስት አወቃቀር የፌደራል ስርአት ነው ብሎ ያምናል፡፡ እውነተኛ የፌደራል መንግስት አወቃቀር ሁሉም የሀገራችን ህዝቦች በስምምነት በመከባበር ተፈቃቅደው ለመኖር የሚያስችል ምቹ አስተዳደራዊ ስርአት ይፈጥራል፡፡ የሚገነባው የፌደራል ስርአት የአስተዳደር ምቹነትን፣ የህዝብ ፍላጎትን፣ ቋንቋና ባህልን፣ መልከዓ-ምድርንና ሌሎች የጋራ እሴቶችን ታሳቢ ያደረገ ይሆናል፡፡
1.6.1 የመንግስት የስራ ቋንቋ
አማርኛና ኦሮምኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ቋንቋ ይሆናሉ፡፡ የፌደራል መንግስቱ አካል የሆኑት የክልል መስተዳድሮች በክልሉ ውስጥ በስፋት ከሚነገሩ ቋንቋዎች ውስጥ አንድ ወይም ከአንድ በላይ ቋንቋዎች የክልል መስተዳድሩ የስራ ቋንቋ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
1.7.1 የሀገር መከላከያ ኃይል
1.7.2 የፖሊስና ደህንነት ኃይል